ስለ
SUNCASA በድሬዳዋ (ኢትዮጵያ)፣ በኪጋሊ (ሩዋንዳ) እና በጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) የአየር ንብረት ለውጥ መላመድንና የብዝኃ ሕይወት ጥበቃን ለማጎልበት በየአካባቢዎቹ ለተለዩ ፍላጎቶችና ቅድሚያ ለሚሰጣቸው ጉዳዮች በቀጥታ ምላሽ በመስጠት እየሠራ ይገኛል። ለተፋሰስ ጥበቃና መልሶ ልማት ሥርዓተ-ጾታን ያማከሉና ተፈጥሮ ላይ መሠረት ያደረጉ መፍትሔዎችን (NbS) ተግባራዊ የሚያደርገው ይህ ዕቅድ የጎርፍ መጥለቅለቅን ጨምሮ ከተሞች ከአየር ንብረት ጋር ተያያዥነት ያላቸው በርካታ ስጋቶችን መቋቋም እንዲችሉ አቅማቸውን ለማጎልበት ያለመ ነው።
ይህ ሥርዓተ-ጾታን ያማከለ NbS ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ ስጋት ባለባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ 2.2 ሚሊዮን አከባቢ ሰዎችን በቀጥታ ተጠቃሚ የሚያደርግ ይሆናል። በተጨማሪም ፕሮጀክቱ በሚተገብራቸው ዘላቂ የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ምክንያት 7 ሚሊዮን የሚሆኑ ነዋሪዎች ኑሯቸው የሚሻሻል ከመሆኑም ባሻገር ከተማዋ የውሃ እጥረትንና ሙቀትን እንዲሁም የመሬት መንሸራተትንና የአፈር መሸርሸርን ለመቋቋም ያላት አቅም ይጨምራል።
SUNCASA ተግባራዊ ከሚያደርጋቸው ተፈጥሮን መሠረት ያደረጉ መፍትሔዎች መካከል በድሬዳዋና በኪጋሊ የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ ማልማት፣ በኪጋሊ የተራቆቱ የከተማ ደን መሬቶችን መልሶ ማልማትና መልሶ ማቋቋም እንዲሁም በጆሃንብሰርግ የጁክስኬይ ወንዝ (put an English name here) ተፋሰስን ወረው የሚገኙ መጤና ተዛማች የዕጽዋት ዝርያዎችን ማስወገድ ይገኙበታል። ከመልሶ ማልማት ተግባራት ጎን ለጎን SUNCASA የተፋሰስና ረግረጋማ አካባቢዎችን የመልሶ ማልማት ሥራ የሚያከናውን ሲሆን የከተማ የዛፍ ሽፋንን በመጨመር በሦስቱም የከተማ የሙቀት ችግርን ለመፍታት ያስችላል።
የምንከተለው ዘዴ
የSUNCASA ስኬት በሦስት ወሳኝ ሐሳቦች ላይ የተመሠረተ ነው። በመጀመሪያ ስለአየር ንብረት ለውጥ ተወራራሽ የሥርዓተ-ጾታ ተጽእኖዎች የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖርና ሥርዓተ-ጾታን ያማከሉና ተፈጥሮ ላይ መሠረት ያደረጉ መፍትሔዎችን በተመለከተ ግልጽነት እንዲዳብር ያደርጋል። ሁለተኛው በየአካባቢዎቹ ያሉ አጋር አካላት ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የተያያዙ ስጋቶችን ለመቅረፍ ተፈጥሮ ላይ መሠረት ያደረጉ መፍትሔዎችን መጠቀም ውጤታማና ከወጪም አንጻር አዋጭ መንገድ መሆኑን የሚቀበሉ መሆናቸው ነው። ሦስተኛው ደግሞ የማዘጋጃ ቤት ኃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት አሁን ያሉት የአስተዳደር ማዕቀፎች ሥርዓተ-ጾታን ያማከሉና ምላሽ ሰጪ እንዲሆኑ ማስተካከያዎችን ለማድረግ ቁርጠኛ መሆናቸው ነው።
ግቦቻችን
የSUNCASA ተነሳሽነት የሚከተሉት ናቸው፡-
- የጎርፍ አደጋን ለመቀነስና አስተማማኝ የውሃ አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ የወንዞችን ተፋሰስ መልሶ በማልማትና በማደስ ሥርዓተ-ጾታን ያማከሉና ተፈጥሮ ላይ የተመሠረቱ መፍትሔዎችን ማዳበርና መተግበር
- ሴቶችና በቂ ውክልና የሌላቸው ቡድኖች በአየር ንብረት መላመድ ውሳኔ አሰጣጥ፣ ዕቅድ፣ አቅርቦትና ክትትል ላይ የሚገጥማቸውን እንቅፋት በማስወገድ የሥርዓተ-ጾታ እኩልነትንና ማኅበራዊ ፍትሕን ማጎልበት
- ዘላቂ መተዳደሪያ እንዲኖር ማድረግና የአካባቢዎቹን ብዝኃ ሕይወት ማሰደግና መጠበቅ
- የአረንጓዴ የሥራ ዕድሎችን መፍጠር
- አረንጓዴ የሕዝብ የጋራ ቦታዎችን በማልማት የማኅበረሰቡን ደኅንነት ማሻሻል
የኛ ቡድን
Benjamin Simmons
Senior Director, Economic Law and Policy
Todd Gartner
Director, Cities4Forests and Natural Infrastructure, WRI
Aklilu Fikresilassie
Director, Thriving Resilient Cities, WRI Africa; Representative of WRI in Ethiopia
Alec Crawford
Director, Nature for Resilience
Alemakef Tassew
Urban Development Project Specialist, WRI Africa
Amanda Gcanga
Country Lead for Urban Water Resilience & Senior Urban Policy Analyst, WRI
Ana Balanean
Policy Advisor, Gender Equality and Social Inclusion
Ayushi Trivedi
Research Associate, Gender and Social Equity, WRI
Cesar Henrique Arrais
Senior Communications Officer
Clare Blackwell
Research Analyst II, WRI
Daniela Facchini
Director, Global Operations and Program Management, WRI Ross Center for Sustainable Cities
David Uzsoki
Lead, Sustainable Finance
Dimple Roy
Director, Water and Director, Manitoba Relations
Eden Takele
Engagement & Communications Specialist, Climate Program and WRI Ross Center for Sustainable Cities, WRI Africa
Hellen Wanjohi-Opil
Resilience African Cities Lead, WRI Africa
Josephine Apajo
Planning, Monitoring and Evaluation Learning Manager, WRI Africa
Liesbeth Casier
Lead, Public Procurement and Sustainable Infrastructure
Lisa Beyer
Urban Water Infrastructure Manager, WRI
Lizzie Marsters
Environmental Finance Manager, Natural Infrastructure, WRI
Lynn Wagner
Senior Director, International Environmental Governance
Marc Manyifika
Country Lead for Urban Water Resilience/Lead Spatial Planner for the program, WRI Africa
Matthew TenBruggencate
Communications Manager
Meghan Stromberg
Urban Resilience Project Coordinator, WRI Ross Center for Sustainable Cities
Michail Kapetanakis
Policy Advisor, Sustainable Infrastructure
Nona Rogava
Project Manager
Pablo Lazo
Director of Urban Development, WRI Ross Center for Sustainable Cities
Richard Grosshans
Lead, Bioremediation
Sadof Alexander
Communications Manager, Cities4Forests, WRI
Samantha Boardley
Associate
Stefan Jungcurt
Lead, SDG Indicators and Data
Tristan Easton
Senior Project Manager