SUNCASA | Woman and man from ARCOS Network planting seedlings in a project nursery in Kigali. (Photo: William Bidibura | ARCOS Network | SUNCASA)

የሥርዓተ ጾታ እኩልነትና ማኅበራዊ አካታችነት

የSUNCASA ፕሮጀክት በድሬዳዋ (ኢትዮጵያ)፣ በኪጋሊ (ሩዋንዳ) እና በጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) ከተሞች የአየር ንብረት ለውጥ ለመቋቋም በሚካሄዱ ተፈጥሮ ተኮር መፍትሄዎች (NbS) ዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራና ክትትል ሥራዎች ላይ የሴቶችንና የሌሎች ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተሳትፎ የሚገቱ ነገሮችን ለመቀነስ ያለመ ነው።

የአየር ንብረትና የብዝኀ ሕይወት መዛባት በሰዎች ኑሮና የሥራ ዕድሎች ላይ የሚያሳርፉት ተጽዕኖ እንደ ጾታቸው እና ተያያዥ የማንነት መገለጫዎች ይለያያሉ። የተቋማዊ መገለል እና አድልኦ ተጠቂ የሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች ብዙውን ጊዜ በአየር ንብረት ለውጥ ተመጣጣኝ ባልሆነ መልኩ ተጎጂ ሲሆኑ ይስተዋላል። በታሪካዊና ባሕላዊ የሥርዓተ ጾታና ማኅበራዊ ልማዶች ሳቢያ በተፈጥሮ ሃብቶች አጠቃቀምና አስተዳደር ረገድ በሴቶችና በወንዶች እንዲሁምወጣቶች መካከል የሚና ልዩነት አለ።

ለምሳሌ ያህል፣ በባህላዊ የሥርዓተ ጾታ ሚናዎች የተነሳ ሴቶች ምግብ እና ውሃ የማቅረብ ኃላፊነት እንዲወጡ ተመጣጣኝ ባልሆነ መልኩ የሚጣልባቸው ሲሆን ይህም በተፈጥሮ ሀብት ላይ ከፍተኛ ጥገኝነት እንዲኖራቸው ያደርጋል።አስተዋጻኦ የሚሰጥ እና ፍትሐዊ እንዲሆን ለማድረግ የSUNCASA ፕሮጀክት እነዚህን የሚና ልዩነቶች፣ ኃላፊነቶችና ዕውቀቶች ከግምት እንዲያስገባና በሌላ በኩልም አግላይ ልማዶችና ተግባራቶችን እንዲዋጋ ታስቦ ተነድፏል። ይህ ተነሳሽነት የማህበረሰብ አባላት በተለይም ወንዶች እና ውሳኔ ሰጪዎች ሥርዓተ ጾታን ኣካታች ለሆኑ የNbS አካሄዶች ያላቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ ይሠራል።

SUNCASA ማኅበራዊ ልማዶችንና የአካባቢያዊ ሥልጣን ክፍፍልን ጨምሮ በሥርዓተ ጾታ ተኮር ላይ የተመሰረቱ እንቅፋቶች ዙሪያ የሚደረጉ ውይይቶች ያመቻቻል። ይህ ተነሻሽነት ሴቶችም ሆኑ ሌሎች ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎችን በውሳኔ ሰጪነት ያላቸውን ተደራሽነት ለማሻሻልና በNbS ተግባራት እና በሁሉም የአስተዳደር እርከን ውስጥ ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚያስችላቸውን አቅም ለመገንባት ያለመ ነው። ከዚህ በተጨማሪም SUNCASA የየከተሞቹ አስተዳደሮች ሥርዓተ ጾታን ከግምት ውስጥ ያስገባ የNbS ሥልቶችን እንዲነድፉ በማገዝ ይበልጥ አሳታፊና የኣከባቢን ሁኔታ ያገናዘበ የፖሊሲ አወጣጥ ሒደት እንዲሰፍን አስተዋጽዖ ያደርጋል።

የSUNCASA ግቦች በሥርዓተ ጾታና ማኅበራዊ አሳታፊነት ረገድ

  • ማኅበራዊ ልማዶችን መታገል፦ የሴቶችንና ሌሎች አነስተኛ ውክልና ያላቸውን ቡድኖች መብቶች የሚያዳብሩ አዎንታዊ ማኅበራዊና ሥርዓተ ጾታዊ ልማዶችን ማበረታታት።
  • ዕድሎችን መፍጠር፦ ሴቶችን እና ሌሎች ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎችን  በNbS ትግበራ ላይ ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዲኖራቸው ማስቻልና በውሳኔ አሰጣጥ ላይ ተደራሽነት ማግኘታቸውን ማረጋገጥ።
  • ድልድዮችን ማበጀት፦ የሴቶች አደረጃጀቶችንና ሌሎች ጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎችን በአካባቢያቸው በሚተገበሩ የNbS ማስተዳደር ሒደቶች ላይ ትርጉም ባለው መልኩ ተሳትፎ እንዲኖራቸው መደገፍና ከዚሁ ጎን ለጎንም የየአካባቢው አስተዳደሮች ኃላፊነት ያለባቸው ከመሆኑ አኳያ ይበልጥ ለሥርዓተ ጾታ እኩልነት ጉዳዮች ምላሽ የሚሰጥ የውሳኔ አሰጣጥ ሥርዓት እንዲተገብሩ ማገዝ።

ከከተማ NbS አንፃር ሦስቱ የሥርዓተ ጾታ እኩልነትና የማህበራዊ አካታችነት (GESI)

SUNCASA | Amharic - GESI